1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በቤኒ ሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተፈናቃዮች ወደ ቄዬአቸው የመመለስ ስራ እና የተፈናቃዮቹ ስጋት

ዓርብ፣ ግንቦት 7 2012

የአማራ  ክልል እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ኮማንድ ፖስት ተፈናቃዎችን ወደ ቀድሞ ቄአቸው እየመለሰ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ዓመት በመተከል እና ጃዊ አካባቢዎች በነበረው ግጭት ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 4008 ሰዎች ወደ ቀድሞ ቀያቸው  መመለሳቸውን የክልሉ የሰላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3cHnV
Karte Äthiopien Metekel EN

በቤኒሻንጉል ክልል ተፈናዮች ወደ ቄዬአቸው እየተመለሱ ነው

የአማራ  ክልል እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ኮማንድ ፖስት ተፈናቃዎችን ወደ ቀድሞ ቄአቸው እየመለሰ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ዓመት በመተከል እና ጃዊ አካባቢዎች በነበረው ግጭት ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል እስካሁን 4008 ሰዎች ወደ ቀድሞ ቀያቸው  መመለሳቸውን የኮማድ ፖስቱ አባል እና የቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል የሰላም ግንባታ እና ጸጥታ በሮ ኃላፊ አቶ አበራ ባያታ ተናግረዋል፡፡ ከማንዱራ ወረዳ ተፈናቅለው በአማራ ክልል ጓንጓ ወረዳ የነበሩ 3433  ተፈናቃወዮች ትናንት ወደ ቀያቸአቸው ተመልሰዋል፡፡ 332 የቁም እንስሳት በኮማንድ ፖስቱ ለባለንብረቶች መመለሳቸውን፣  97 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ቀስትን ጨምሮ አምስት ሺ(5000) ድምጽ አልባ መሳሪያዎችም  መያዛቸውን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ

ታምራት ዲንሳ

አዜብ ታደሰ