1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሲዳማ ዞን ግጭት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 25 2011

በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው  ግጭት ተጠርጥረው የተያዙ ግለሰቦች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

https://p.dw.com/p/3NBLE
Äthiopien Hawassa | Oberster Gerichtshof
ምስል DW/S. Wegayehu

የፍርድ ቤት ውሎ

የመርማሪ ፖሊስ ግለሰቦቹን በሀዋሳ ከተማና በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት በተከሰቱ ሁከቶች ለጠፋው የሰው ሕይወትና ንብረት ጠርጥሪያቸዋለሁ ሲል ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ጉዳያቸው ከሕግ ይልቅ  ፖለቲካዊ ይዘት ያለውና ምንአልባትም በበላይ ኃላፊዎች ትዕዛዝ የተፈጸመ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። የችሎቱን ውሎ የተከታተለው የሐዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ተጨማሪ ዘገባ ልኮልናል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ