1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሰኔ 15ቱ ግድያ የተጠረጠሩ የክስ መከላከያ አሰሙ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 1 2012

የክስ መከላከያ ካቀረቡት መካከል በቀድሞዉ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በጀነራል ሰዓረ መኮንን ገዳይነት የተጠረጠረው የአስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ እና የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ይገኙባቸዋል።

https://p.dw.com/p/3Udfq
Justitia mit Pendelwaage
ምስል picture-alliance/Ulrich Baumgarten

የፍርድ ቤት ውሎ

ባለፈው ዓመት ሰኔ 15 ቀን በአማራ ክልል ተሞከረ ከተባለው መፈንቅለ መንግሥት እንዲሁም በአዲስ አበባ በከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ላይ በተፈፀመው ግድያ ጋር በተያያዘ የተከሰሱ 13 ተጠርጣሪዎች በዛሬው ዕለት የክስ መቃወሚያቸውን አቀረቡ። የክስ መከላከያ ካቀረቡት መካከል በቀድሞዉ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በጀነራል ሰዓረ መኮንን ገዳይነት የተጠረጠረው የአስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ እና የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ይገኝባቸዋል። ተከሳሾቹ የክስ መቃወሚያቸውን ያቀረቡት ለፌደራል የፀረ ሽብር እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ የሚፈፀም ወንጀል አንደኛ ችሎት መሆኑን ከአዲስ አበባ ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የላከልን አጭር ዘገባ ያመለክታል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ