1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሰሜን ኢትዮጵያ እየተስተጓጎለ ላለው የዕርዳታ ተደራሽነት የመንግስት ምላሽ

ቅዳሜ፣ ጥር 14 2014

በትግራይ ለሚስተዋለው ሰብዓዊ ቀውስ እና የእርዳታ ቁሳቁሶች እጥረት ዋነኛ ተጠያቂው በሰሜን ኢትዮጵያ መንግስትን የሚፋለመው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መሆኑን የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ፡፡

https://p.dw.com/p/45xEO
Äthiopien Regierung reagiert auf humanitäre Krise
ምስል Seyoum Getu/DW

በሰሜን ኢትዮጵያ ለተሰተጓጎለው የሰብአዊ ዕርዳታ አቅርቦት መንግስት ምላሽ ሰጥቷል

በትግራይ ለሚስተዋለው ሰብዓዊ ቀውስ እና የእርዳታ ቁሳቁሶች እጥረት ዋነኛ ተጠያቂው በሰሜን ኢትዮጵያ መንግስትን የሚፋለመው ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መሆኑን የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) በሳምንቱ መጨረሻ ባወጣው ሳምንታዊ ሪፖርቱ በጦርነት ለተጎዳዉ የትግራይ ሕዝብ የሚሰጠዉ የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ እየተሟጠጠ መሆኑን አስታወቋል።

 አስተያየታቸውን ለዶይቸ ቬለ የሰጡት የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ መንግስት የእርዳታ ቁሳቁሶች ወደ ትግራይ እንዲገቡ ከረጂ ተቋማት ጋር ብርቱ ጥረቶችን እያደረገ ቢሆንም ህወሓት  ግጭት በማስነሳት የእርዳታ ማስተላለፊያ መንገዶችን እንደሚዘጋ ገልጸዋል፡፡

ስዩም ጌቱ

ታምራት ዲንሳ