1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሞጣ ከተማ ጥቃት ለተቃጠሉ መስጊዶች ርዳታ

ዓርብ፣ ጥር 22 2012

በሞጣ ከተማ ጥቃት ለተቃጠሉ መስጊዶችና የንግድ መደብሮች ማሠሪያ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ዛሬ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች ተከናውኗል። ለዚህ ተግባር ሕዝበ ሙስሊሙ ድጋፍ እንዲያደርግ በሚል ጥሪ ተደርጎ የቆየ ሲሆን፤ ሕዝቡ ከስግደቱ ጎን ለጎን ገንዘብ በመለገስ ድጋፉን አሳይቷል።

https://p.dw.com/p/3X6MP
Äthiopien Addis Abeba | Muslime sammeln Geld zum wiederaufbau niedergebrannter Moscheen
ምስል DW/S. Muchie

ክርስቲያን ወገኖችም ድጋፍ ሲያደርጉ ነበር

ዛሬ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች በሞጣ ከተማ ጥቃት ለተቃጠሉ መስጊዶችና የንግድ መደብሮች ማሠሪያ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴተከናውኗል። ለዚህ ተግባር ሕዝበ ሙስሊሙ ድጋፍ እንዲያደርግ በሚል ጥሪ ተደርጎ የቆየ ሲሆን፤ ሕዝቡ ከስግደቱ ጎን ለጎን ገንዘብ በመለገስ ድጋፉን አሳይቷል። የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ሰለሞን ሙጬ በትልልቆቹ የፒያሳው ኑር መስጊድ እና የፍል ውኃው ቶፊቅ መስጊዶች የገንዘብ ማሰባሰብ ተግባሩን ተመልክቷል። በገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብሩ ላይ ክርስትያን ወገኖችም ድጋፍ ሲያደርጉ እንደነበር ተገልጧል። ወጣቶች «ለሞጣ» የሚሉ ጽሑፎች የተለጠፉባቸው ካርቶኖችን ይዘው ገንዘብ ሲሰበስቡም ተመልክቷል። 

ሰለሞን ሙጬ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ