1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በመረጃ ፍሰቱ ላይ የሚታየው ክፍተት

እሑድ፣ ሐምሌ 25 2013

ጉዳዩ የሀገር እና የዜጎች የደህንነት ጉዳይ እንደመሆኑም የተቀናጀ እና የሰከነ የመረጃ ፍሰት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በዚህ ወቅት አስፈላጊ መሆኑን የሚያመለክቱ ወገኖች ኅብረተሰቡን ግራ ከመጋባትና ከስጋት ለማዳን የመረጃ ፍሰቱን ሥርዓት ማስያዝ እንደሚያስፈልግ ይመክራሉ።

https://p.dw.com/p/3yL3F
Symbolbild Störungen von Übertragungssignalen
ምስል DW/ttjana; Matthias Enter - Fotolia.com

እንወያይ

ካለፈው ጥቅምት ወር መጨረሻ አንስቶ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገረው ጦርና የጦርነት ወሬ ብቻ መስሏል። እንዲህ ያለው ስጋት ባጠላበት ወቅት ዜጎች ተገቢና የተጣራ መረጃ እንዲያገኙ የማረግ ኃላፊነት የመንግሥት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በዚህ ረገድ የመረጃ ክፍተት መኖሩ ጥቂት የማይባለው የኅብረተሰብ ክፍል ዘመን ያመጣለትን ስልት ተጠቅሞ ያልተጣሩ ወሬዎች ወደሚናፈሱባቸው የማኅበራዊ ትስስር ዘዴዎች ትኩረቱን እንዲያደርግ አስገድዷል። በዚህ ደግሞ ያልተጣሩ ሀገራዊ ጉዳዮች መናፈሳቸው ኅብረተሰቡ የደህንነት ስጋት እንዲሰማው ማድረጉን ታዛቢዎች ይናገሩታል። ጉዳዩ የሀገር እና የዜጎች የደህንነት ጉዳይ እንደመሆኑም የተቀናጀ እና የሰከነ የመረጃ ፍሰት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በዚህ ወቅት አስፈላጊ መሆኑን ይመክራሉ። በመረጃ ፍሰቱ ላይ የሚታየው ክፍተት እና ተጠያቂትን የቃኘ ውይይት ዶቼ ቬለ አካሂዷል፣ በውይይቱ ከተነሱት ነጥቦች የሚከተሉት ይገኙበታል።

ሸዋዬ ለገሠ