በለንደን ማራቶን ኢትዮጵውያኑ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ወጡ
እሑድ፣ ሚያዝያ 14 2010ማስታወቂያ
በብሪታንያ ለንደን ዓመታዊው የማራቶን ውድድር በሀገሬው አቆጣጠር ረፋዱን ተካሄዷል፡፡ በዚህ ውድድር ያሸንፋሉ በሚል ሲጠበቁ የነበሩት ኢትዮጵያውያኑ ቀነኒሳ በቀለ እና ጥሩነሽ ዲባባ ድል ከእነሱ ጋር አልሆነም፡፡ ቀነኒሳ ውድድሩን በስድስተኛነት ሲያጠናቅቅ ጥሩነሽ ውድድሩን አቋርጣ ወጥታለች፡፡ ከውድድሩ በኋላ ቀነኒሳ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገረው ሩጫው ከጅማሬው አንስቶ መፍጠኑ ለውጤቱ መበላሸት ዋንኛው ምክንያት ነው።
ቀነኒሳ እና ጥሩነሽ እንዳሰቡት ባይሳካላቸውም በውድድሩ የተሳተፉት ሌሎች ኢትዮጵያውያን ከአሸናፊዎች ዝርዝር መግባት ችለዋል፡፡ ቶላ ሹራ ሁለተኛ ኬንያዊውን ኢሉውድ ኪፕቼጌን ተከትሎ ሁለተኛ ወጥቷል። ብሪታንያዊው ሞ ፋራህ በደጋፊዎቹ ፊት ሶስተኛ ሆኖ ጨርሷል። ሆኖም የብሪታንያን የማራቶን ሪከርድ ሰብሯል።
በሴቶች ድል የቀናቸው ኬንያውያን ሆነዋል። በአምስት ሺህ እና አስር ሺህ ሜትር ውድድር የኢትዮጵያውያን ብርቱ ተፎካካሪ የሆነችው ቪቪያን ቼሮይት የሀገሯን ልጅ ብሪጅድ ኮስጊን አስከትላ ገብታለች። ኢትዮጵያዊቷ ታደለች በቀለ ደግሞ ሶስተኛ ሆናለች፡፡
ውድድሩን በስፍራው ሆና ከተከታተለችው የለንደኗ ወኪላችን ሀና ደምሴ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ሀና ደምሴ
ተስፋለም ወልደየስ