1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሶስት ረመዳን በመጠለያ፤ ሶስት ኢድ በመጠለያ

እሑድ፣ ግንቦት 16 2012

ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በድሬዳዋ የተጠለሉ 4800 ገደማ ኢትዮጵያውያን ረመዳንን ለሶስተኛ ጊዜ በመጠለያ ፆመዋል፤ ኢድን መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸው ሳይሟሉ በመጠለያ ሲያከብሩ ይኸ ለሶስተኛ ጊዜ መሆኑ ነው

https://p.dw.com/p/3cgwB
Äthiopien  Äthiopische Vertriebene in Dire Dawa
ምስል DW/M. Teklu

ሶስት ረመዳን በመጠለያ፤ ሶስት ኢድ በመጠለያ

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ  ማግስት በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት ተፈናቅለው ድሬደዋ የተጠለሉ ከአራት ሺህ በላይ ዜገች ሶስት አመታትን በመጠለያ ማሳለፍ ግድ ሆኖባቸዋል። ለሶስተኛ ጊዜ የረመዳን የፀም ወቅትን በመጠለያው ማሳለፋቸውን የሚናገረው የመጠለያው አስተባባሪ አቶ ቦቆሬ ሀሰን በተለይ ዛሬ የተጠናቀቀው የረመዳን ወቅት ከባድ እንደነበር ገልጿል።

Äthiopien  Äthiopische Vertriebene in Dire Dawa
ምስል DW/M. Teklu

 «ከዛሬ ነገ ከመጠለያ ወጥተን ወደ መደበኛ ህይወት እንሸጋገራለን» በሚል ተስፋ ሶስት አመታትን በመጠለያው ያስቆጠሩት እነዚህ ተፈናቃዮች ከአንድ ሺህ በላይ ህፃናቶቻቸው ትምህረት እየተማሩ አለመሆናቸውንም አቶ ቦቆሬ ተናግረዋል።

Äthiopien  Äthiopische Vertriebene in Dire Dawa
ምስል DW/M. Teklu

 «በቅርብ ጊዜ መፍትሄ ታገኛላችሁ» ከሚል የዘለለ ዛሬም የተጨበጠ ነገር አለመኖሩን የሚናገረው አቶ ቦቆሬ በቅርቡ መፍትሄ ይደረጋል መባሉን እንደሰማ ተናግሯል፡፡

 የድሬደዋ አደጋ ስጋት ቅነሳ ማስተባበርያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ለእነዚህ ዜጎች ዘላቂ መፍትሄ የመስጠት ሓላፊነት የሶማሌ ክልል መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡ ከክልሉ ሃላፊዎች ጋር በተካሄደ ውይይት ከረመዳን ፆሙ በኃላ የማቋቋም ስራ እደሚሰራ ተናግረዋል።

መሳይ ተክሉ

እሸቴ በቀለ