ሩዋንዳ 500 ስደተኞችን ከሊቢያ ልትቀበል ነው
ረቡዕ፣ ጳጉሜን 6 2011ማስታወቂያ
«የአፍሪቃውያንን ችግር በአፍሪቃውያን መፍታት» በሚል መርኅ ሩዋንዳ በሊቢያ የሚገኙ ስደተኞችን ተቀብላ ለማስተናገድ በአፍሪቃ ኅብረት የሦስትዮሽ ሠነዱን አጸደቀች። በመጀመሪያው ዙርም ከተለያዩ የአፍሪቃ ሃገራት ወደ ሊቢያ ሩዋንዳ 500 ስደተኞችን ከሊቢያ ልትቀበል ነው።
ተሰደው መፈናፈኛ ያጡ 500 ስደተኞችን ሩዋንዳ ለመቀበል ወስናለች። ሩዋንዳ ለሕፃናት እና ታዳጊ ዕድሜ ላይ ለሚገኙ ስደተኞች ቅድሚያ መስጠቷንም የሩዋንዳ አምባሳደር ወይዘሮ ሆፕ ቱምኩንዴ ጋሳቱራ ተናግረዋል። የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት እስካሁን 42 ሺህ ግድም ስደተኞችን እንደመዘገበ፤ ኹኔታዎችም ከአቅሙ በላይ መኾኑን ገልጧል። በዚህ ወቅት ሩዋንዳ አብነት ኮና አፍሪቃውያን ስደተኞችን ከሊቢያ ለመቀበል መወሰኗን አወድሷል። ለዝርዝሩ ጌታቸው ተድላ ኃይለ-ጊዮርጊስ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ-ጊዮርጊስ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ