1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሥለ አዲሱ የካቢኔ አባላት የሕዝብ አስተያየት

ሐሙስ፣ ጥቅምት 8 2011

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አሕመድ በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ ምናልባት በአፍሪቃም ለመጀመርያ ጊዜ የሆነ ያሉትን ግማሽ በግማሽ  ሴቶችን ያካተተውን አዲስ የካቢኔ አባላትን ለምክር ቤት አቅርበዉ ካፀደቁ ወዲህ ከአገር አልፎ የዓለም መነጋገርያ ሆንዋል።

https://p.dw.com/p/36nJH
Äthiopien - Parlament
ምስል DW/Y. Gebregziabher

«ጥሩ ዉጤት ያመጣሉ ብለን እናምናለን»

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፉት ዓመታት ምክር ቤቱ በተደጋጋሚ የሴቶች ተሳትፎ በሚገባቸዉ ልክ እንዲሆን ጥያቄ ሲቀርብ በመቆየቱን ማስታወሳቸዉ ይታወቃል። 20 አባላት ያሉበት ከአዲሱ ካቢኔ 10ዎቹ ሴቶች ናቸዉ። በዚህም የሴቶች የአመራርን ሚና አጠናክሮ ለመቀጠል ሴቶች ከሌላ ጊዜ በተለየ ሁኔታ ቁልፍ የሚንስትር ቦታዎችን እንዲይዙ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ መንግሥት የመከላከያ ሚኒስትር ሴት ናቸዉ። አዲሱን አካቢኔ ሹመት በተመለከተ የባሕርዳሩ ወኪላችን የሕዝብ አስተያየትን አሰባስቦ ልኮልናል። 


አለምነዉ መኮንን
አዜብ ታደሰ
ሸዋዬ ለገሠ