1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መንግሥት የቬንትሌተር እጥረትን እንዲፈታ ተጠየቀ

ሰኞ፣ መጋቢት 28 2012

ኢትዮጵያ ቬንትሌተር የሚባለው መሳሪያ ብዙም እንደሌላትና ያለውም ለኮሮና ተጠቂዎች ብቻ ሳይሆን በሌሎች በሽታዎች ጽኑ ህክምና ውስጥ ለገቡትም እንደሚውል የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ተናግሯል። የመሳሪያው ዋጋ ውድ ቢሆንም አሁን ከተለያየ ወገን ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚገኘው ድጋፍ ለዚሁ እቃ ግዥ ቢውል የሚል የባለሙያዎች ምክርም ጎልቶ እየተደመጠ ነው

https://p.dw.com/p/3aYRL
Deutschland Krankenhausärzte erhalten Anweisungen zu einem Beatmungsgerät am Universitätsspital Eppendorf in Hamburg
ምስል picture-alliance/AP Photo/A. Heimken

መንግስት በኮሮና ተኅዋሲ ለሚጠቁ ጽኑ ህሙማን እጅግ አስፈላጊ የሆነውን የትንፋሽ መስጫ መሳሪያ እጥረት በቻለው አቅም እንዲፈታ ጥሪ ቀረበ። ኢትዮጵያ ይህ ቬንትሌተር የሚባለው መሳሪያ ብዙም እንደሌላት እና ያለውም ለኮሮና ተጠቂዎች ብቻ ሳይሆን በሌሎች በሽታዎች ጽኑ ህክምና ውስጥ ለገቡትም እንደሚውል የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ተናግሯል። የመሳሪያው ዋጋ ውድ ቢሆንም አሁን ከተለያየ ወገን ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚገኘው ድጋፍ ለዚሁ እቃ ግዥ ቢውል የሚል የባለሙያዎች ምክርም ጎልቶ እየተደመጠ ነው።ዝርዝሩን የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰሎሞን ሙጬ ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ 
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ