መንግሥት ስለ ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትና ህወሓት ወታደራዊ ጥምረት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 6 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጀው ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በማለት የሚጠራው እና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው ቡድን ከህወሓት ኃይሎች ጋር ወታደራዊ ጥምረት ፈጥሬያለሁ ብሏል።በዚህ ላይ መልስ እንዲሰጥ የተጠየቀው መንግስት በበኩሉ «ይህንን ቀድሜ ነው የማውቀው» ሲል መልሷል። የኦሮሚያ ክልል ባለሥልጣናት ከዶይቼ ቬለ ጋር በነበራቸው ቆይታ ጥምረቱ የተለየ ጫና እና ግፊት እንደማይፈጥርባቸውም ተናግረዋል። ስዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ ተጨማሪ ዘገባ ልኮልናል።
ስዩም ጌቱ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ