1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚ

 መቀሌ፣ የዋጋ ንረት 

ዓርብ፣ ጥር 10 2011

ሸማችና ሺያጮች እንደሚሉት በተለይ የእርሻ ምርትና የሥጋ እንስሳት ዋጋ አለቅጥ ጨምሯል።አምና በዚሕ ወቅት 500 ብር ይሸጥ የነበረዉ አንድ ኩንታል በቆሎ ዘንድሮ 800 ብር ገብቷል።

https://p.dw.com/p/3Bmll
Äthiopien landwirtschaftliche Erzeugnisse auf einem Markt
ምስል DW/M. Haileselassie

(Beri- Mekelle) Tigray-Price hike on agricultural products - MP3-Stereo

ትግራይ ርዕሠ ከተማ መቀሌ ዉስጥ የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ መምጣቱን የከተማይቱ ነዋሪዎችና ነጋዴዎች አስታወቁ።ሸማችና ሺያጮች እንደሚሉት በተለይ የእርሻ ምርትና የሥጋ እንስሳት ዋጋ አለቅጥ ጨምሯል።በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተዉ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና የኤርትራ ሸማቾች ወደ ኢትዮጵያ መግባት ለዋጋዉ ንረቱ እንደምክንያት ይጠቀሳሉ።የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለስላሴ እንደዘገበዉ አምና በዚሕ ወቅት 500 ብር ይሸጥ የነበረዉ አንድ ኩንታል በቆሎ ዘንድሮ 800 ብር ገብቷል።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

ተስፋለም ወልደየስ