መቀሌ በግጭት ማግሥት
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 15 2013ማስታወቂያ
ላለፉት ሁለት ወራት ግድም ተዋጊ ጄትና ሄሊኮብተርና የጦር አዉሮፕላኖች ሲያጉረመርሙበት የነበረዉ የመቀለ ሰማይ ዛሬ የመንገደኞች አዉሮፕላን ድምፅ ተሰምቶበታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ52 ቀናት በፊት አቋርጦት የነበረዉን የከና ወደ መቀሌ በረራ ዛሬ ጀምሯል። የትግራይ ርዕሠ-ከተማ አጠቃላይ እንቅስቃሴም እየተረጋጋ ነው። ስልክ፣ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ የመድሐኒት መደብሮችና ታክሲዎች ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል አገልግሎት እየሰጡ ነው። ሸቀጥም ወደ ከተማይቱ እየገባ ነው። ነዳጅ ማደያዎች፣ ባንኮችና አብዛኞቹ ሱቆች ግን አሁንም ዝግ ናቸው። ፖሊስ ጣቢዎችና ፍርድ ቤቶችም ዝግ ናቸው። ለአንድ ወር ያሕል መዘገብ አቋርጦ የነበረዉ የመቀሌው ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴም ዛሬ ሥራ ጀምሯል። በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ