1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕወሓት ከ20 መኪና ርዳታ ውጪ አልደረሰንም አለ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 27 2014

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ትግራይ ክልል ከገቡ 20 ርዳታ የጫኑ መኪኖች ሌላ የደረሰ ርዳታ እንደሌለ በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ዐስታወቀ። ከረዥም የውዝግብ ጊዜ በኋላ 20 ሰብአዊ ርዳታ የጫኑ መኪኖች መቐለ የደረሱት ባሳለፍነው ዓርብና ቅዳሜ ነበር።

https://p.dw.com/p/49VBk
Äthiopien Mekelle | WFP Nahrungsmittellager
ምስል Million H. Silasse/DW

«6 ሚልዮን ገደማ የሚሆን ሕዝብ ርዳታ ይሻል»

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ወደ ትግራይ ከገቡ 20 ርዳታ የጫኑ መኪኖች በኋላ ሌላ የደረሰ ርዳታ እንደሌለ በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ዐስታወቀ። የትግራይ ሰብአዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ዶክተር አትንኩት መዝገቡ፦ በትግራይ አለ ያሉትን ሰብአዊ ቀውስ ለማቃለልና ለወራት የተስተጓጐለውን የርዳታ አቅርቦት ሥራ ለማካካስ በየቀኑ 300 ርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ትግራይ ክልል ሊደርሱ ይጠበቁ ነበር ብለዋል። ከረዥም የውዝግብ ጊዜ በኋላ 20 ሰብአዊ ርዳታ የጫኑ መኪኖች መቐለ የደረሱት ባሳለፍነው ዓርብና ቅዳሜ ነበር። እነዚህን ተከትለው ወደ ትግራይ ይጓዛሉ ተብለው የነበሩ ሌሎች ርዳታ የጫኑ 35 መኪኖች እስካሁን ወደ ክልሉ አለመድረሳቸው ተገልጿል። እንደ የትግራይ ክልላዊ መንግስት መረጃ በትግራይ 6 ሚልዮን ገደማ የሚሆን ሕዝብ የሕይወት አድን ሰብአዊ ርዳታ ይሻል። 

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ 
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ