1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለዩክሬን ዳግም ግንባታ መዋጮ

ሐሙስ፣ ሰኔ 15 2015

ለንደን-ብሪታንያ በተሰየመዉ የገንዘብ መዋጮ ጉባኤ ላይ ከፍተኛዉን ገንዘብ ለመስጠት ቃል የገቡት ዩናይትድ ስቴትስ የአዉሮጳ ሕብረትና ብሪታንያ ናቸዉ

https://p.dw.com/p/4SxG2
Ukraine Rave-Aufräumarbeiten in Yahidne, Chernihiv
ምስል Anna Pshemyska/DW

«ቃል የተገባዉ ገንዘብ ወደ 7 ቢሊዮን ይደርሳል» ዩክሬን

የዩክሬንን መንግስት የሚያስታጥቁት ምዕራባዉያን መንግስታት በጦርነት የወደመዉን የዩክሬንን የመሠረተ ልማት አዉታር መልሶ ለመገንባት ወደ 7 ቢሊዮን ዶላር እያዋጡ ነዉ።ለንደን-ብሪታንያ በተሰየመዉ የገንዘብ መዋጮ ጉባኤ ላይ ከፍተኛዉን ገንዘብ ለመስጠት ቃል የገቡት ዩናይትድ ስቴትስ የአዉሮጳ ሕብረትና ብሪታንያ ናቸዉ።ዩክሬንና ሩሲያ የገጠሙት ጦርነት በተፋፋመበት በዚሕ ወቅት ለዳግም ግንባታ ገንዘብ መዋጣቱ አንዳድ ታዛቢዎችን ግራ ማጋባቱ አልቀረም።ሥለገንዘብ መዋጮዉ የብራስልስ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ