ሁለተኛዉ ዙር የችግኝ ተከላ ዘመቻ
ዓርብ፣ ግንቦት 28 2012ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት «የአረንጓዴ አሻራ» ያለዉ ሁለተኛዉ ዙር የችግኝ ተከላ ዘመቻ ዛሬ ሐዋሳ ዉስጥ በይፋ ተጀመሯል።ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ መስተዳድር ባለስልጣናትና የሐገር ሽማግሌዎች በጀመሩት በዘንድሮዉ ክረምት ዘመቻ 5 ቢሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዷል።ዘመቻዉ የኮሮና ተሕዋሲን ስርጭት ለመከላከል ከሚወሰደዉ ርምጃና ጥንቃቄ ጋር አይቃረንም ነዉ የተባለዉ።ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ አምና ባነሳሱትና ባስጀመሩት ዘመቻ አምናን ጨምሮ በ4 ዓመታት ዉስጥ 20 ቢሊዮን ችግኞች ለመትከል ታቅዷል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ዛሬ እንዳሉት አምና ከተተከለዉ ችግኝ 84 በመቶዉ ፀድቋል።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ነጋሽ መሐመድ
እሸቴ በቀለ