78ኛው የኢትዮጵያ የድል በዓል
እሑድ፣ ሚያዝያ 27 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የጥንት አርበኞች ወራሪዉን የኢጣሊያ ጦር ድል ያደረጉበት 78ኛ ዓመት ዕለት ዛሬ ተከበረ። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው የድል ሀውልት ዙሪያ በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔርና የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የበላይ ጠባቂ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፤ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማሕበር ፕሬዝደንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፣ አርበኞችና ቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል። የአድዋ ድልን ጨምሮ አዲስ የመታሠቢያ አደባባይ እንደሚታነፅም በስነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።
ወይዘሮ ሳሕለ ወርቅ ለእድምተኛዉ ባደረጉት ንግግር ዕለቱን፣ በኢትዮጵያዉን መካከል ልዩነት ቢኖርም በሐገር ጉዳይ ልዩነት እንደሌላቸዉ ያስመሰከሩበት ነዉ ብለዉታል።በበዓሉ ላይ የተካፈሉ ጥንታዊ አርበኞች በበኩላቸዉ የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ለሐገሩ ነፃነትና ክብር የነሱን አርዓያ እንዲከተል አደራ ብለዋል።ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ቅኝ ለመግዛት ከወረረችበት ከ 1928 ጀምሮ ድል ሆና እስከተባረረችበት እስከ 1933 ድረስ ኢትዮጵያዉያን አርበኞች ለነፃነታቸዉና ለክብራቸዉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበትን ዉጊያና ትግል አድርገዋል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ልደት አበበ