1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

73 ኛዉ የኢትዮጵያ የአርበኞች የድል ቀን መታሰብያ

ዓርብ፣ ግንቦት 8 2006
https://p.dw.com/p/1BxfT

የኢትዮጵያ አርበኞች፤ ለሃገር ነጻነት፣ አንድነትና ክብር፤ የኢጣልያ ፋሽስት ወራሪ ሃይልን በመመከት፤ ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች በመጉረፍ ጠላትን ያስጨነቀበት እና ድል ያደረገበት አልበገር ባይነትን ያስመሰከሩበት «የኢትዮጵያ ጥንታዊ ጀግኖች አርበኞች የድል ቀን መታሰብያ» ሚያዝያ 27፤ ለ73 ኛ ግዜ ተከብሮአል። ጥንታዊ ጀግና አርበኞች የጣልያንን ጦር አምስት ዓመት ተጋድለዉ የሃገር ነፃነትን ማስከበራቸዉ፤ አኩሪ ድል የመቀዳተቻዉን ታሪክ ህያዉ አድርጎ ለማቆየት፤ የአሁኑ ትዉልድ በተለያዩ ስነ-ፅሁፎች፤ በሙዚቃና ቀረቶዎች፤ በዉዝዋዜና በአልባሳት እንዲሁም በፊልም እና ትያትርን በመሳሰሉ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሲያስታዉስና ታሪክ ሲማማርበት ይታያል።

አዜብ ታደሰ