1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ፖለቲካእስያ

40 ቀኑን የያዘው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት

ሰኞ፣ መጋቢት 26 2014

ካልተጠበቀው የዓለም ክፍል ባልተጠበቀ ሰዓት የፈነዳው የዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ከተጀመረ 40 ቀን ሞላው። ጦርነቱ ከውድመት ኪሳራው ባሻገር በዓለም አቀፍ እና የኃይል አሰላለፍ አኳያ ያለውን ተጽዕኖ እንዴት ይታያል?

https://p.dw.com/p/49S4y
Ukraien, Bucha | Ein Mann geht an einem zerstörten russischen Panzer vorbei
ምስል Serhii Nuzhnenko/AP/picture alliance

ማሕደረ ዜና፤ 40 ቀኑን የያዘው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት

ካልተጠበቀው የዓለም ክፍል ባልተጠበቀ ሰዓት የፈነዳው የዩክሬን ሩሲያ ጦርነት ከተጀመረ 40 ቀን ሞላው። በእነዚህ 40 ቀናት በርካታ የዩክሬን ከተሞች ወድመዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ሞተዋል፤ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ተሰደዋል ወይም ከመኖሪያ ቤት አካባቢያቸው ተፈናቅለዋል። የተመድ እንደሚለው ከሀገር ውጪ የተሰደዱት ቁጥራቸው ከአራት ሚሊየን አልፏል። ጦርነቱ ሩሲያ ዩክሬን ላይ የከፈተችው ጦርነት ቢሆንም ብዙዎች ግን ከዩክሬን ጀርባ ምዕራብ ሃገራት እንዳሉ በመጥቀስ ዓለም በሁለት ጎራ ተከፍሎ እንደሚፋለም ነው የሚቆጥሩት። ማኅደረ ዜና 40 ቀኑን የያዘው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከውድመት ኪሳራው ባሻገር በዓለም አቀፍ እና የኃይል አሰላለፍ አኳያ ያለውን ተጽዕኖ ይመለከታል።

ገበያው ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ