ሥጋት የጋረደዉ የኢትዮጵያ-ሶማሌ አርብቶ አደሮች የአኗኗር ዘይቤ
ደምሳሹ «ሙሊያ»
በአፍሪቃ ቀንድ በተከሰተዉ ድርቅ የኅብረተሰቡን ማንነት የተመሠረተበትና የአኗኗር ዘይቤዉን ቀይሮአል የቀንድ ከብቶችን ሁሉ አዉድሟል። በዚህ አካባቢ ከ600, 000 በላይ የሚገመቱ የቀንድ ከብቶች ሞተዋል። «እንዲህ ያለ ነገር በጭራሽ አጋጥሞኝ አየዉቅም» ይላል የ65 ዓመቱ አርብቶ አደር ኤልቴስ ሙሴ ባሃ ። «ይህንን ድርቅ ሙሊያ ብለን ሰይመነዋል ይላል ሙሴ። ይህ ማለት ደግሞ መሬት ላይ ያለን ሁሉ ነገር የሚደመስስ ነገር ማለት ነዉ»