«የጦር መሳርያ የመቀማት ዓላማ የለንም » ፖሊስ
ሰኞ፣ ጥቅምት 29 2014ማስታወቂያ
«የጦር መሳርያ የመቀማት ዓላማ የለንም » ፖሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ የጦር መሳርያ የማስመዝገቡ ሂደት የከተማዋን ደህንነት ለማስጠበቅ እንጂ የጦር መሳርያ የመቀማት ዓላማ እንደሌለው የከተማዋ ፖሊስ ገለጸ። በትግራይ ተወላጆች ላይ በጅምላ እስራት እየተፈጸመ ነው የሚለውን ክስ እንደማይቀበሉ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል። «ከፖሊስ ጋር ተባብረው የሚሰሩ እና ለፖሊስ መረጃ የሚሰጡ የትግራይ ተወላጆች አሉ» ያሉት ኮማንደር ፋሲካ የከተማዋን ደህንነት የማስጠበቁ ስራ በደሴ እና የኮምቦልቻ ከተሞች የተፈጠረውን አይነት ተመሳሳይ ችግር አዲስ አበባ ውስጥ እንዲከሰት ስለማንፈልግ ቁጥጥራችንን ጠበቅ አድርገናል ብለዋል ።
ነጋሽ መሐመድ አነጋግሯቸዋል።