ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ድጋፍ ለማሳየት በተካሔደ ሰልፍ ድምጻዊ ታሪኩ ጋንካሲ "ሽምግልና ይሻላል" የሚል ጥሪ አቀረበ። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ታዳሚ በተገኘበት ሰልፍ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "እንነሳ፤ የመከላከያ ሠራዊታችንን እንቀላቀላቸው፤ አብረናቸው እንቁም" የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት በድርድር እንዲቋጭ ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙት ጄፍሪ ፌልትማን ባለፈው ሳምንት መፍትሔ ካልተበጀ አገራቸው ማዕቀብ ልትጥል እንደምትችል ጥቆማ ሰጥተዋል። በአዲስ አበባ በተካሔደ ሰልፍ ላይ የአጎዋን ጉዳይ የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች አቤቤ "ዕርዳታ እና ብድር ነጻነታችንን የሚገፈን ከሆነ፤ነጻነታችንን አንገብርም" ብለው ነበር