ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በኤስኦኤስ የህጻናት ማሳደጊያ መንደር መስራች ሔርማን ገማይነር ስም የተሰየመው የዕርዳታ ድርጅት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢዎች አራት ሚሊዮን ዩሮ መደበ። ገንዘቡ በኤስኦኤስ ኢትዮጵያ በኩል በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ማኅበረሰቦች ለመደገፍ ይውላል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች እየተፈጸሙ ያሉትን ግድያዎች ገለልተኛ አካል ጣልቃ ገብቶ በማጥናት ይፋ እንዲያወጣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባት (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንገር (ኦፌኮ) ጠየቁ።
በአፋር ክልል በተደጋጋሚ በተስተዋለው ጦርነትና ድርቅ ሳቢያ በምግብ እጥረት ወደ ሆስፒታል ከገቡ ህጻናት ከ30 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው ማለፉን ሆስፒታሉ አስታወቀ፡፡ ባለፉት ጢቂት ወራት በምግብ እጥረትና በሌሎች ህመሞች ወደ ዱብቲ ሪፌራል ሆስፒታል የሚመጡ ታካሚዎች ቁጥር ከሆስፒታሉ አቅም በላይ ሆንዋል ተብሎአል።
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት 338 ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ። መንግሥት ሰኔ 11 ቀን 2014 በተፈጸመው ጥቃት ስለተገደሉ ሰዎች ቁጥር መረጃ ሲያቀርብ የመጀመሪያ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪ ቢልለኔ ስዩም ዛሬ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለቻ ሰጥተዋል።