ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ለሰሜን ኢትዮጵያው የዓመት ከመንፈቅ ጦርነት የሰላም አማራጮች የቀረቡ ቢመስሉም አሁንም ጦርነቱ ሊያገረሽ እንደሚችል ምልክቶች መታየታቸው እየተገለፀ ነው። ጉዳዩን የሚከታተሉት ባለሙያ ለዶይቼ ቬለ እንደገለጹት፤ ጦርነቱን አሁንም በሰላማዊ አማራጭ የመቋጨት መንገድ ሙሉ በሙሉ ባይዘጋም ነገሮች የሚያሳዩት ስለ አይቀሬው ሌላኛው ምዕራፍ ጦርነት ነው፡፡
የሰብዓዊ መብት ድጋፍ ያለምንም ገደብ እና መደናቀፍ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ። ይሁንና የድጋፍ ሰጪዎች እጥረት እና በመላው ኢትዮጵያ የተረጂዎች ቁጥር መብዛት ሰብዓዊ ድጋፍ በተሟላ ሁኔታ ለማድረስ እክል መፍጠሩን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
« በ2009 ዓ ም ደግሞ ኢትዮጵያ “ከልጅነት ልምሻ ነፃ”ተብላ የምስክር ወረቅት አግኝታ ነበር ሆኖም በ2011 ዓ ም በፖሊዮ ቫይረስ የተጠቃ አንድ የሶማሌላንድ ሰው ወደ ሶማሌ ክልል በመግባቱ ቫይረሱ በቀላሉ በመሰራጨቱ በአማራ፣ኦሮሚያ፣ ድሬዳዋና ሌሎች አካባቢዎች በቀላሉ ተዳርሷል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የተጠናከረ ክትትልና ክትባት ሲሰጥ ነበር ።»
የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ኃይሎች ተቆጣጥረውት ከቆዩባቸው የአፋር ክልል፤ ዞን ሁለት፤ ስድስት ወረዳዎች መውጣታቸውን ቢገልጹም፤ የአከባቢው ነዋሪዎች እና የአፋር ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ጉዳዩን አስተባብለዋል። የሕወሓት ኃይሎች በአንዳንድ የአፋር ቀበሌዎች እንደሚገኙ እና የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማም አስተያየት ሰጪዎቹ ተናግረዋል።