ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ማሊ ጂሃዲስቶችን ከሚዋጋው (G5) ከሚታወቀዉ የሳህል ሀገራት ጥምረት እና የዓለም አቀፍ ጥምር ጦር ኃይል ቡድን ራስዋን ማግለልዋን ገለፀች። እንደ ጎርጎረሳዉያኑ አቆጣጠር በ 2014 ዓ.ም ማሊ ሞሪታንያ፤ ቡርኪናፋሶ፤ ኒጀር እና ቻድ ተባብረዉ ጂ 5ን በመመስረት በጎርጎረሳዉያኑ 2017 ዓ.ም ጥምር ጦር ማቋቋማቸዉ ይታወሳል።
ኢትዮ-ቴሌኮም ዓለም የደረሰበትን አምስተኛው ትውልድ ወይም 5ጂ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት አዲስ አበባ ውስጥ በተመረጡ አምስት ሥፍራዎች ላይ አስጀመረ። አገልግሎቱ የአገርን እድገት በቴክኖሎጂ ለማገዝ ታልሞ የተጀመረ መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል።
በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች እሁድ ሚያዚያ 23 ቀን፣2014 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር የነበረዉ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ለዘጠኝ ቀናት የነበረበት አድራሻ ጠፍቶ ቆይቶ ትናንት እራሱን ቤቱ ደጃፍ ላይ እንዳገኘ ገለፀ። በጤንነቱ ላይ ምንም ነገር እንዳልደረሰም ባስተላለፈዉ የጽሑፍ መልክት ተናግሮአል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮ ለሁለተኛ ጊዜ ምርጫ ካሸነፉ በኋላ የመጀመያ የውጭ ጉብኝታቸው ወደ በርሊን አድርገዉ፤ ከጀርመኑ መራሔ መንግሥት ኦላቭ ሾልዝ ጋር በሩሲያ ዩክሬንን ወረራ ላይ እየተወያዩ ነው። ሁለቱ ሃገራት "ከዩክሬን ጋር እንደ አውሮጳውያን ቤተሰብ ጎን ለጎን እንቆማለን ብለዋል።