ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎች ማኅበር መንግሥት ለመገናኛ ብዙኀን ችግሮች መፍትሄ እንዲሰጥ ለጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ደብዳቤ ላከ። ማኅበሩ የመገናኛ ብዙኀን ባለሙያዎች ከቤታቸውና ከሥራ ገበታቸው በጸጥታ ኃይሎች መታፈናቸው እንዳሳሰበው፤ ጠ/ሚሩ ይህን ከፍተኛ የሕግ ጥሰት ሰምተው እንዳልሰሙ መሆናቸው እንዳሳዘነዉ ለጠ/ሚሩ ደብዳቤ ፅፎአል።
ከቅርብ ግዚያት ወዲህ እየተበራከተ የመጣው የግለሰቦች የሰባዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ኢሰመጉ አታወቀ። ድርጅቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ግለሰቦች ከየቦታው ተጠልፈዉ ለተውሰኑ ቀናት የት እንደደረሱ አለመታወቁ እና ኃለፊነቱን የሚወስድ አካል አለመኖሩ ከፍተኛ የሰባዊ መብት ጥሰት ብቻ ሳይሆን የግለሰቦችን ህገ-መንግስታዊ መብትን መቃወም ነው ብልዋል።
በሰላም እጦት ፣ በግጭት፣ በድርቅ እና በውጭ ምንዛሪ እጥረት እየፈተነ ያለው የኢትዮጵያ የግብርና ክፍል ኢኮኖሚ ከእነ ችግሮቹም ቢሆን የምርት እድገት ያልተለየው መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ተናገረ። ሚኒስቴሩ ይህ ዘገባ የትግራይ ክልልን እንደማይጨምር አውስቷል።
የመንግሥት እርምጃዎች ኢትዮጵያ ልትሸከመው ወደማትችል አለመረጋጋት እንደሚያስገቧት ፓርቲዎች አስጠነቀቁ። የአብን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ እናት ፓርቲና መኢአድ መንግሥት "አፈና" እየፈጸመ ነው ሲሉ ከሰዋል። የመንግሥት ኮምዩንኬንሽ አገልግሎት እንደሚለው ግን የፀጥታ ኃይሎች የሚወስዷቸው እርምጃዎች "ህግ የማስከበር" ዓላማ ያላቸው ናቸው