የድንጋይ ንጉሱ እና ጥንታዊዉ የመገበያያ ገንዘብ
ሰኞ፣ መጋቢት 17 1999ማስታወቂያ
ከአክሱም ዉድቀት በኳላ የኢትዮጽያ ስልጣኔ ያልጠፋ ቢሆንም እስከ አስራ ዘጠነኛዉ ምዕተ አመት መጨረሻ ድረስ አንድም ገንዘብ ያሳተመ ንጉስ እንዳልነበር ጥናቶች ያስራዳሉ። በኢትዮጽያ የጨዉ ገንዘብ ማለት አሞሌ ከሺህ አመት በላይ በግብይት ሂደት ዉስጥ የገንዘብ ሚና ሲጫወት እንደነበር መናገር ይቻላል። በኢትዮጽያ አሞሌ ጨዉ የማርትሪዛ ብር የኢንግሊዝ ሽልንግ ከዚያም አልፎ ጥይት የመገበያያ ገንዘብ እንደነበር ይታወሳል። አንጋፋዉ ጋዜጠኛ እና ደራሲ ማሞ ዉድነህ የኢትዮጽያን የጥንት የመገበያያ ዘዴ ያወጉናል።