ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በኦሮሚያ ያሉትን የስኳር አምራች ፋብሪካዎችን እየፈተነ የሚገኘው የፀጥታ ችግር በምርቱ የገበያ ላይ እጥረት ካስከተሉ አበይት ምክኒያቶች ናቸዉ፡፡ በዚሁ ችግር በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጥቃት ደርሶበት ሁለት ጊዜ ስራ ያቆመዉ የአርጆ ዴዴሳ ስኳር ፋብሪካ በፀጥታ ችግሩ መፈተኑ ይጠቀሳል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እስከ ግንቦት 30 2015 ዓ.ም በክልሉ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረበ፡፡ በምርጫ ቦርድ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀረበ የተባለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክረ ሀሳብ እንዳልደረሰው ጠቋሟል፡፡
በአዲስ አበባ የቤቶች ፈረሳ በቅጽበት ቤት አልባ ያደረጋቸው ነዋሪዎችን በእንባ አራጭቷል፤ ሕጻናት ተማሪዎች፤ እናቶችና አረጋውያንንም ለጎዳና መዳረጉ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚዎች አነጋጋሪ ሆኗል ። የከተማዪቱ ከንቲባ «ከፍተኛ ፍልሰት»ን «መንግሥትን በመጣል በኃይል ሥልጣን» ከመቆጣጠር ጋር አያይዘው መናገራቸው በርካቶችን አስቆጥቷል ።
ትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት አመሰራረት ላይ እምነት እንደሌላቸው ሦስት ፓርቲዎች ተናገሩ።