1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚአፍሪቃ

የዋጋ ግሽበት ቁጥጥር በድሬደዋ እና በሶማሌ ክልል

ሐሙስ፣ ሐምሌ 29 2013

በመሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ የተፈጠረውን ከፍተኛ የዋጋ ንረት ተከትሎ የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዳቸውን የሶማሌ ክልል እና ድሬደዋ አስተዳደር ባለሥልጣናት አስታወቁ። በድሬደዋ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከሁለት መቶ በላይ የችርቻሮ መሸቻ ሱቆች እና 11 መጋዘን መታሸጉ ተሰምቷል።  

https://p.dw.com/p/3yb30
Äthiopien | Dire Diwa | Geschlossene Läden
ምስል Mesay Teklu/DW

«ከመቶ በመቶ በላይ የዋጋ ጭማሪ መታየቱ»

የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ከድር ጁሀር በአስተዳደሩ የከፋ ሆኗል ያሉትን የዋጋ ግሽበት ለመቆጣጠር በተወሰደ እርምጃ ከሁለት መቶ በላይ የችርቻሮ መሸጫ ሱቆች እና 11 መጋዘን መታሸጉን ተናግረዋል። በቀጣይ የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበራትን ከማጠናከር ባለፈ በመሠረታዊ ሸቀጦች ላይ የመሸጫ ዋጋ ትመና እንደሚደረግም ተናግረዋል።  

Äthiopien | Dire Diwa | Geschlossene Läden
የታሸቀ መደብርምስል Mesay Teklu/DW

በነጋዴው ዘንድ በሚታየው የሸቀጥ አላስፈላጊ ክምችት ማድረግ እና በጥቁር ገበያ በሚካሄድ የምንዛሪ ሴራ ለዋጋ ግሽበቱ መባባስ ምክንያት ናቸው ያሉት የሶማሌ ክልል የንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አህመድ ቦባን በበኩላቸው በዚህ ላይ የክልሉ ካቢኔ ያሳለፈውን ውሳኔ ለዶይቸ ቬለ በስልክ ገልፀዋል። ከቅርብ ቀናት ወዲህ በፍጥነት ተለዋዋጭ በሆነው የሸቀጦች ዋጋ በአብዛኞቹ ላይ ከመቶ በመቶ በላይ ጭማሪ ማሳየቱ ነው የተገለጸው።

መሳይ ተክሉ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ