ከ 12 ተኛዉ እስከ 20ኛዉ ክፍለ ዘመን በብራና ላይ የተፃፉ የኢትዮጵያ የክርስትናና የእስልምና ጥንታዊ የእጅ ጽሑፎች ላይ የተደረጉ ጥናቶችን በንጽጽር ያቀረበና የታሪክ ምሁራን የተሳተፉበት ዐውድ ጥናት
ባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ ፈረንሳይ መዲና ፓሪስ ላይ ተካኺዷል። የሁለቱ ሐይማኖቶች ጥንታዊ የብራና ላይ የእጅ ጽሑፎች፤ ከነበራቸዉ ሐይማኖታዊ ፋይዳ ባሻገር በወቅቱ የነበረዉን የእጅ ጽሑፍ ግንኙነት እና መወራረስ እንዲሁም ባህርይ ላይ በታሪክ ምሁራኑ ተዳሰዋል። በተጨማሪ ጽሑፎች ታሪክ ነጋሪነታቸዉና ጥበባዊ ፋይዳቸዉም ጭምር በምሑራኑ ትኩረትን አግኝተዋል። ፓሪስ ላይ ለሁለት ቀናት በተካሄደዉ መድረክ ላይም ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዉ ነበር። በሁለቱ ቀን ዝግጅት ላይ ተገኝታ የነበረችው፤ የፓሪሷ ዘጋቢአችን ሃይማኖት ጥሩነህ ፣ ተከታዩን ዘገባ ልካልናለች።
ሐይማኖት ጥሩነህ
ተክሌ የኋላ