የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ለሕወሃት ኃይሎች የሰጠው ማሳሰቢያ
ቅዳሜ፣ ጥቅምት 27 2014ማስታወቂያ
በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር(ኦነግ) “ህወሀት ወደ ኦሮሚያ ክልል የሚያደርገውን ግስጋሴ” እንዲገታ ጠየቀ፡፡
ከሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም. የኢትዮጵያ መንግስት የተናጥል የተኩስ አቁም ውሳኔ ወዲህ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በተስፋፋው የትግራዩ ጦርነት ሕወኃት ሰሞኑን በአማራ ክልል ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞችን ተቆጣጥሮ ወደ መሃል አገር እንደሚገሰግስ አሳውቆ ነበር፡፡ይህንኑን ተክትሎም ነው ኦነግ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ ሕወኃት “የኦሮሞ ህዝብን ሉዋላዊነት እንዲያከብር እና የጦር ሀይላቸውን ወደ ኦሮሚያ ድንበር ውስጥ ከማስገባት እንዲቆጠቡ” ሲል ያሳሰበው።የፓርቲው ቃል አቀባይ ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ አሁን ላይ በትግራዩ አማጺያን እና መንግስት መካከል የሚካሄደውን ጦርነት ትርጉም አልባ በማለት የሚደረጉ የክተት ጥሪዎችንም ነቅፈዋል፡፡
ስዩም ጌቱ
ታምራት ዲንሳ