ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ኢትዮጵያ ዛሬ ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባን ጨምሮ ጋዜጠኞች፣ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ተቺዎች፣ አቀንቃኞች፣ ባለሐብቶችና ሌሎች ዜጎችም በጠራራ ፀሐይ የሚታገቱ፣ የሚደበደቡ፣ የሚዘረፉባት፣ ፖለቲከኞች፣ምሑራን፣ጋዜጠኞች፣የኃይማኖት መሪዎች፣ የመብት ተሟጋቾች ሳይቀሩ ጎሳና ኃይማኖት እየመረጡ እርስበርስ የሚካሰሱ፣የሚወዛገቡባት ሐገር ናት።
"የዚህ ጦርነት ተሳታፊዎች ብዙ ናቸው። ዓላማቸውም እንደዚሁ በጣም የተለያየ ነው። ትግራይ ላይ ወይም ሕወሓት ላይ ተመሳሳይ አቋም የነበራቸው አካላት አብረው ተሰልፈዋል እና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እነዚህን አካላት አሁንም አንድ ላይ አስተባብሮ ወደ ሰላም ስምምነቱ ማስገባት እና ተገዢ ለማድረግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ይገባኛል"
ከ1960ዎቹ ጀምሮ የሚዘከረዉ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ታሪክ፣ከ1980ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የሚነገረዉ የኤርትራ የሐገርነት ታሪክም የሱና የሳቸዉ ሚና ካልታከለበት በርግጥ ጎደሎ ነዉ።ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ።ለኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም አኞ ጠላት ናቸዉ።ገንጣይ።ለመለስ ዜናዊ ግን መላዕክም-ሰይጣናም ብጤ ናቸዉ።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳደር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትናንት መሾማቸው የተገለጠው አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነትን ለማስጠበቅ እንደሚሠሩ ተናገሩ ። የተፈናቀሉ ያሏቸውን መልሶ ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ተግባራት እና ሌሎች ቀዳሚ አጀንዳዎችን እንደሚሠራባቸውም ዐስታውቀዋል ።