የኢህአዴግ መደበኛ ስብሰባ እና የተሰጡ አስተያየቶች
ማክሰኞ፣ ጥር 7 2011ማስታወቂያ
ከረቡዕ ጥር 8 ጀምሮ የሚካሄደዉ የኢህአዴግ መደበኛ ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ፤ ከአራቱ የግንባሩ አባላት የተዉጣጡ ተሳታፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይሁንና የግንባሩ አባላት እርስ በርስ ያላቸዉ ግንኙነት እምብዛም በመሆኑ ከስብሰባዉ የተለየ ነገር አይገኝም የሚሉ ብዙዎች ቢሆኑም፤ ስብሰባዉ የአራቱን ግንባር አባላት ወደ አንድ ጠረቤዛ በማምጣቱ በአገሪቱ አሁን በሚታየዉ ለዉጥ የሚታየዉን ቅራኔ ለመፍታት ጥሩ እድል ይሆናል ብለዉ የሚገምቱም ጥቂቶች አይደሉም። የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለስላሴ ነገ ስለሚጀመረዉ የኢህአዴግ መደበኛ ስብሰባ በመቀሌ የተለያዩ ነዋሪዎችን አስተያየት አሰባስቦ ልኮልናል።
ሚሊዮን ኃይለሥላሴ