ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
አንዱ የፌስቡክ እድምተኛ ጠቅላያችን ስለ ተባበሩት አረብ ኤምረትስ መሆን አለበት ሚያወሩት እንጂ ስለ ኢትዮጵያ እንዲህ በድፍረት አይሞክሩትም ሲሉ ሌላዉ፤ የሰላም ተምሳሌት የኖቤል ተሸላሚው መሪያችን እንኳን ለኢትዮጵያ ለዓለም የሚተርፍ እውቀት ያላቸዉ እውቀቱንም በተግባር ያሳዩ መሪ ብለዉ አስተያየት ሰጥተዋል።
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በኦሮሚያ ያሉትን የስኳር አምራች ፋብሪካዎችን እየፈተነ የሚገኘው የፀጥታ ችግር በምርቱ የገበያ ላይ እጥረት ካስከተሉ አበይት ምክኒያቶች ናቸዉ፡፡ በዚሁ ችግር በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጥቃት ደርሶበት ሁለት ጊዜ ስራ ያቆመዉ የአርጆ ዴዴሳ ስኳር ፋብሪካ በፀጥታ ችግሩ መፈተኑ ይጠቀሳል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እስከ ግንቦት 30 2015 ዓ.ም በክልሉ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረበ፡፡ በምርጫ ቦርድ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቀረበ የተባለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክረ ሀሳብ እንዳልደረሰው ጠቋሟል፡፡
በአዲስ አበባ የቤቶች ፈረሳ በቅጽበት ቤት አልባ ያደረጋቸው ነዋሪዎችን በእንባ አራጭቷል፤ ሕጻናት ተማሪዎች፤ እናቶችና አረጋውያንንም ለጎዳና መዳረጉ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚዎች አነጋጋሪ ሆኗል ። የከተማዪቱ ከንቲባ «ከፍተኛ ፍልሰት»ን «መንግሥትን በመጣል በኃይል ሥልጣን» ከመቆጣጠር ጋር አያይዘው መናገራቸው በርካቶችን አስቆጥቷል ።