ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የ2014 ዓ.ም ፈተና ቦታ አዲስ መሆኑ የተወሰነ መደናገጥ ቢፈጥርም ተማሪዎቹ በሰላም ፈተናቸውን መውሰዳቸውንም አመልክተዋል፡፡ “የእኛ ተማሪዎች ዘንድሮ ፈተና የወሰዱት ዩኒቨርሲቲ ነው ተፈተኑት፣ ተቀላቅለው አዳራሽላይ ስለነበር የተፈተኑት ትንሽ መደናገጥ ነበር፣ ግን ፈታኞቹና የፀጥታ አካላት ተንከባክበዋቸው ተረጋግተው በሰላም ተፈትነዋል፡፡”
የ86 ዓመቱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ይህን ጉዞዋቸዉን ለማድረግ ያቀዱት ከስድስት ወራት በፊት ቢሆንም በአደረባቸዉ የጤና እክል ምክንያት ከእቅዳቸዉ ግማሽ ዓመት ዘግይተዉ ነዉ፤ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፤ ኪንሻሳ የደረሱት። ወደ አንድ ሚሊዮን ነዋሪ እንደሚገኝባት በሚገመተዉ መዲና የኪንሻሳ፤ ፍራንሲስን ለመቀበል በነቂስ ወጥቶም ነበር።
የኬንያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሞት ቅጣትን በሃገሪቱ ለመሻር እንቅስቃሴ ጀምሯል። ምንም እንኳን የሞት ቅጣት አሁንም በኬንያ ህጋዊ ቢሆንም ወንጀልን በመዋጋት ረገድ ውጤታማ አለመሆኑን እና ድሆች ላይ ብቻ ማነጣጠሩን የኬንያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አጽኖት ሰጥቷል። በኬንያ የመጨረሻው የሞት ቅጣት የተፈፀመዉ ከ 35 ዓመታት በፊት ነዉ።