ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የምዕራባውያን ሃገራትን ትኩረት የሳበው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ የሚገመተው የኔቶ በምሥራቅ አውሮጳ አባላቱን የማብዛት እንቅስቃሴ የተገታ አይመስልም። ለሩሲያ የምትጎራበተው ፊንላንድና ስዊድንም የኔቶ አባል ለመሆን መነሳታቸው በኪየቭ ሞስኮ መካከል የተጫረውን የጦርነት እሳት አድማስ እንዳያሰፋው የሚሰጉ ጥቂት አይደሉም።
የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO)፣ የአዉሮጳ ሕብረትና የቡድን ሰባት (G7) አባል ሐገራት መሪዎች የጀመሩት ጉባኤ አብይ ትኩረት የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ መከላከል ነዉ
የተቦዳደሱ ሕንፃዎች፣የነደዱ፣ የተሰባበሩ፣ የተመነቃቀሩ የቤት ቁሳቁሶች፣ የተጨረማመቱ መኪኖች፣የተፈረካከሱ ባቡር ጣቢያዎች፣ ፋብሪካዎች፣ የነደዱ ታንክ-መድፍ፣የጦር ተሽከርካሪዎች-ከሁሉም በላይ የተዘረረ አስከሬን፣ የተኮማተረ የሰዉ አካል፣የኪየቭ፣የኻሪኪቭ፣የኸርሰን፣የማርዮፖል፣ የቡቻን የሌሎችም የዩክሬን ከተሞች ገፅታ።የዩክሬን ሕዝብ ምፅዓት።
ባይደን አዉሮጳ ላይ «የዘባረቁትን» ለማስተባበል ሹማምቶቸዉ ከዋሽግተን ሸብ-ረብ ማለታቸዉ አልቀረም።ጥፋቱን መጠገን ግን የቻሉ አይመስልም።የሞስኮዎች ቁጣ ከመንተክተኩ በፊት የፓሪሶች ትችት ቀደመ።ብራስልስ ላይ የተረጋገጠዉ ፅኑ አንድነት ስንጥቅ-ጭረት እንዳማያጣዉ ተረጋገጠም።