ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ቡድን 7። የምጣኔ ሐብት ቀዉስ የወለደዉ፣በምጣኔ ሐብታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር፣ ምጣኔ ሐብታዊ ስብስብ ነበር።የዩናይትድ ስቴትሱ የገንዘብ ሚንስትር ጆርጅ ሹልስ የያኔ ዉጥናቸዉ ዛሬ የደረሰበትን ቢያዩ የሚሉትን ከመጠየቅ ባለፍ በርግጥ አናዉቀዉም።
ፀሎት፣ ምሕላ፣ ተማፅኖ ጥሪዉ ጦርነቱን ለማስቆም አይደለም የማስቆም ተስፋ እንኳን ለመፈንጠቅ አቅመቢስ መሆኑ ነዉ ቀቢፀ-ተስፋዉ።የሕይወት፣ የሐብት፣ንብረት ጥፋቱም የተፋላሚ ኃይላት መሪዎችን ልብ የሚያራራ አልመሰለም
የምዕራባውያን ሃገራትን ትኩረት የሳበው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ የሚገመተው የኔቶ በምሥራቅ አውሮጳ አባላቱን የማብዛት እንቅስቃሴ የተገታ አይመስልም። ለሩሲያ የምትጎራበተው ፊንላንድና ስዊድንም የኔቶ አባል ለመሆን መነሳታቸው በኪየቭ ሞስኮ መካከል የተጫረውን የጦርነት እሳት አድማስ እንዳያሰፋው የሚሰጉ ጥቂት አይደሉም።
የአውሮፓ ኅብረት አባል አገራት ከሩሲያ ከሚሸምቱት ነዳጅ ሁለት ሶስተኛውን ለማገድ ከስምምነት ደርሰዋል። ውሳኔው ከሩሲያ በባሕር የሚጓጓዘውን ነዳጅ ብቻ የተመለከተ ነው። የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ቻርልስ ሚሼል እና የጀርመን መራሔ-መንግሥት ኦላፍ ሾልዝ ሩሲያ ለውጊያ ከዘመተችበት ዩክሬን እንድትወጣ ጫና ያሳድራል ብለው ተስፋ አድርገዋል።