ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በአዲስ አበባ የቤቶች ፈረሳ በቅጽበት ቤት አልባ ያደረጋቸው ነዋሪዎችን በእንባ አራጭቷል፤ ሕጻናት ተማሪዎች፤ እናቶችና አረጋውያንንም ለጎዳና መዳረጉ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚዎች አነጋጋሪ ሆኗል ። የከተማዪቱ ከንቲባ «ከፍተኛ ፍልሰት»ን «መንግሥትን በመጣል በኃይል ሥልጣን» ከመቆጣጠር ጋር አያይዘው መናገራቸው በርካቶችን አስቆጥቷል ።
የትናንቱ የድምፅ አሰጣጥ ሒደት በተወሰኑ አካባቢዎች ካጋጠሙ መለስተኛ ችግሮች በስተቀር በታቀደው መሠረት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡
የባሌ ገበሬዎች በሕዳር እና ታኅሣስ ወራት እስከ 4,200 ብር ያወጣ የነበረው አንድ ኩንታል ስንዴ በ3,200 ብር ለመሸጥ በመገደዳቸው ቅሬታ ገብቷቸዋል። አንድ የጋሰራ ወረዳ ገበሬ "የመኪና፣ የሠራተኛ ወጪ ሲታሰብ ምንም ትርፍ የለውም። ዞሮ ዞሮ መንግሥት ያተርፍ እንደሆነ ነው እንጂ አርሶ አደር ተጎጂ ነው" ሲሉ ቅሬታቸውን አስረድተዋል።
የቡድን 20 አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በሣምንቱ መጨረሻ የኢትዮጵያ የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ “በፍጥነት እንዲጠናቀቅ” ጥሪ አቅርበዋል። ወደ 27 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ዕዳ ያለበት የኢትዮጵያ መንግሥት በአከፋፈል ረገድ ሽግሽግ ለማድረግ ጥያቄ ያቀረበው በሐምሌ 2013 ቢሆንም እስካሁን ድርድሩ ፈቅ አላለም