ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ኃይሎች ተቆጣጥረውት ከቆዩባቸው የአፋር ክልል፤ ዞን ሁለት፤ ስድስት ወረዳዎች መውጣታቸውን ቢገልጹም፤ የአከባቢው ነዋሪዎች እና የአፋር ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ጉዳዩን አስተባብለዋል። የሕወሓት ኃይሎች በአንዳንድ የአፋር ቀበሌዎች እንደሚገኙ እና የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማም አስተያየት ሰጪዎቹ ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ትግራይ ክልል ከገቡ 20 ርዳታ የጫኑ መኪኖች ሌላ የደረሰ ርዳታ እንደሌለ በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ዐስታወቀ። ከረዥም የውዝግብ ጊዜ በኋላ 20 ሰብአዊ ርዳታ የጫኑ መኪኖች መቐለ የደረሱት ባሳለፍነው ዓርብና ቅዳሜ ነበር።
የሰብዓዊ መብት ድጋፍ ያለምንም ገደብ እና መደናቀፍ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ። ይሁንና የድጋፍ ሰጪዎች እጥረት እና በመላው ኢትዮጵያ የተረጂዎች ቁጥር መብዛት ሰብዓዊ ድጋፍ በተሟላ ሁኔታ ለማድረስ እክል መፍጠሩን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ሰሞኑን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት እና የትግራይ ክልልን በሚያስተዳድረው የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) በኩል ግጭት ስለማቆም ውሳኔ በተናጠል መሰጠቱን አስመልክተው የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል። ነዋሪዎች ውሳኔው አሳሳቢ ሰብአዊ ሁኔታን ለማቃለል አጋዥ ሊሆን ይችላል ብለዋል። በተፈፃሚነቱ የተጠራጠሩም አልጠፉም።