ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ሰሞኑን በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚዎችን እያነጋገሩ ነው። በዋናነት የበርካቶችን ትኩረት በሳቡ ሦስት ጉዳዮች ላይ ከተሰጡ አስተያየቶች የተወሰኑትን መራርጠናል።
«ምክረው ምክረው እንቢ ካለ መከራ ይመክረው የሚለው አባባል ሲገባቸው ተመልሰው ተስማምተዋል ከዚህ ጥፋት መማር አለባቸው» «እነሱስ አይደለም 1.5 ትሪሊዬን ፣ 1ብር ከሀምሳ ሳንቲም የጠፋባቸውም አይመስሉም» «ሀገሪቱንና ህዝቡን ለዚህ ችግር የዳረጉት ተጠያቂ መሆን አላባቸው ።»
«ህገ መንግስቱ መነካት የለበትም የሚሉና ተቀዶ ይጣል የሚሉት ሁለቱም ፅንፍ የያዙ አስተሳሰቦች ናቸው። ህገመንግስቱ ከጥቅማቸው ጉዳታቸው የሚያመዝኑ አንቀፆች መቀየር አለባቸው በሚለው እንስማማለን፤ »ብለዋል። ሌላው ደግሞ «ጥናቱ ተአማኒነት ይጎድለዋል! ምክንያቱም ሀገሪቱ በቀለጠ ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ወቅት የተደረገ በመሆኑ ነው !» ብለዋል።
የኦሮምያ ክልል መንግሥት በክልሉ ለሚደረገዉ የሰላም ጥረት ድጋፍ መጠየቁ፤ ስድስት ወራት የሞሉት የፕሪቶርያ ስምምነት አተገባበር ፍጥነት ይጎድለዋል መባሉ፤ ጉምቱዉ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌዉ ወደ ሃገር ቤት ሊመለሱ መሆኑ እንዲሁም በ 32 ቋንቋዎች የሚራጨዉ ዶቼ ቬለ 70ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑ በተሰኙ ርዕሶች ስር የተሰጡ ርዕሶችን ጨምቀን ይዘናል።
በሰዉ እጅ የተገደሉ የገዢዉ ፓርቲ ፖለቲከኛ ሽኝትና የመገደላቸዉ ሰበብ-፣ የጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ማስጠንቀቂያ፣ የኢትዮጵያ መንግስትና የኦሮሞ ነፃ አዉጪ ሠራዊት (ኦነሠ) ድርድር የተስፋና ቀቢፀ-ተስፋ ቃርጮሽ፣ የጀርመኑ መራሔ መንግስት የኢትዮጵያ ጉብኝትና በጎ-መጥፎ መልዕክቱ
ለሰላም ድርድሩ መሳካት እዉቅና የተሰጣቸዉ ሰዎች ጉዳይ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት «ኦነግ ሸኔ» ከሚለው እና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከሚለው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚያደርገው የሰላም ድርድር ፣የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች የመቀሌ ጉብኝት እንዲሁም የሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ በዚህ ሳምንት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ያነጋገሩ ጉዳዮች ናቸው።
የመናገር ነጻነት ይከበር፤ የታሰሩ ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የቀረ በጥሪ ለመጀመርያ ጊዜ ነቀምት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ እንዲሁም በሱዳን ጦር ሠራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይል መካከል ተጠናክሮ የቀጠለዉ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ ሱዳናዉያንን ወደ ጎረቤት ሃገር እያሰደደ መሆኑ ስር የተሰጡ አስተያየቶችን ይዟል።
የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና «ለማደራጀት» የሚለው ውሳኔ በአማራ ክልል ለተከታታይ ቀናት ከፍተኛ ተቃውሞና ሕዝባዊ ቁጣ አስተጋብቷል ። ብልጽግና ፓርቲ የአማራ ሕዝብ ለጥቃት ተጋላጭ በሆነበት ወቅት ልዩ ኃይሉን ትቅጥ አስፈትቶ ለመበተን እየሞከረ ነው ሱሉ በርካቶች በብርቱ ተቃውመዋል ። የጋዜጠኞች እስርም ቀጥሏል ። አስተያየቶችን አሰባስበናል ።