ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በዛሬው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ቅኝት መሰናዶ፦ የሰሜን ሸዋው ጥቃት፤ የሲኖዶስ ሕገወጥ የጳጳሳት ሹመት የቀሰቀሰው ቁጣ እንዲሁም የአቶ በረከት ስምዖን መፈታት ላይ እናተኩራለን። አስተያየቶቻችሁ የተሰባሰበበትን ጥንቅር ሙሉ ዘገባ በድምፅ ማድመጥ ይቻላል።
የአዲስ አበባ ከተማ የወሰን አከላለል፣የመንግስት የሰላም የድርድር ምክረ ሃሳብ እና የህወሃት ክስ እንዲሁም በደቡብ ክልል የተነሳው የክልልነት ጥያቄ እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ በዚሀ ሳምንት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በርከት ያሉ አእስተያየቶች የተሰጡባቸው ጉዳዮች ናቸው።
«ከኃላፊነታቸው መነሳት መልቀቅ ብቻ ሳይሆን የነበራቸው ኃላፊነት ላይም ላጎደሉት የፍትህ ስርዓት ሁሉ የድርሻቸውን መጠየቅ አለባቸው። ፍትህ ሳይረጋገጥ ዘላቂ ሰላም አይታሰብም።» «ድሬዳዋ ራሷን ችላ መካለል አለባት እንጂ ወደየትኛውም ክልል መካለል የለባትም።»«እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፍቅር ሰላም አንድነት የኢትዮጵያን ይሁን»
የኢድ አል-ፊጥር በዓል አዲስ አበባ ሲከበር አንድ ፖሊስ «በስሕተት» አፈነዳዉ የተባለ አስለቃሽ ጢስ መዕምናን ማስደንገጡና ማተራመሱ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት 7.2 ሚሊዮን ቤቶች በ10 አመታት ለመገንባት የያዘው ውጥን በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መነጋገሪያ ነበሩ። የፕሬስ ነጻነት ቀን ሲከበር በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ጉዳይ ተነስቷል።