1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሙኒክ የዓለም የፀጥታ ጉባኤ

ዓርብ፣ ጥር 24 2005

በዓለም አቀፋዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ የሚነጋገረው የሙኒክ የፀጥታ ጉባኤ ዛሬ ማምሻውን ተጀምሯል። ለ3 ቀናት የሚቆየው ይኽው ጉባኤ በማሊእና በሶሪያ እንዲሁም በሌሎች ብጥብጥ ባየለባቸው ሃገራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይነጋገራል።

https://p.dw.com/p/17WpP
ምስል Reuters

ወደአራት መቶ የተገመቱ ታዳሚዎችን የሚያስተናግደዉ ዓመታዊዉ የሙኒክ ዓለም ዓቀፍ የፀጥታ ጉባኤ ዛሬ ማምሻዉን ተጀምሯል። ጉባኤዉ በተለይ የማሊ እና የሶርያ ቀዉስ ላይ ትኩረቱን ማድረጉን ከስፍራዉ የወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። በጉባኤው ላይ መራህያነ መንግሥትና ርዕሳነ ብሄራትን ጨምሮ 70 የሚሆኑ የመከላከያ ሚኒስትሮችና የጦር መሣሪያ ኢንዱስትሪና የልዩ ልዩ የንግድ ተቋማት መሪዎች በአጠቃላይ ወደ 400 እንግዶች ተካፋይ ናቸው። ከተሳታፊዎቹ አንዱ የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ናቸው።

Logo der Münchner Sicherheitskonferenz

ባይደን በነገው እለት ከአትላንቲክ ወዲህና ወዲያ ማዶ ባሉት ግንኙነቶች በሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ቃል ኪዳን ድርጅት በእንግሊዘኛው ምህፃር NATO ና ሩስያ ግንኙነት እንዲሁም ስለ ህንድና ብራዚል ፈጣን እድገት በሚካሄደው ንግግር ላይ ይካፈላሉ። ዛሬ ጀርመን የገቡት ባይደን ከጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ጋር በርሊን ውስጥ በሁለቱ አገራት የንግድ ግንኙነት ላይ እንደሚመክሩም ተዘግቧል። ባይደን ነገ ከጀርመን ወደ ፈረንሳይ በማቅናት ሰኞ ከፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ ጋር ፓሪስ ውስጥ ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ባይደን ምክትል ፕሬዝዳንት ከሆኑ ወዲህ ጀርመንን ሲጎበኙ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ነው። በሌላ በኩል ባይደን ለአንድ የጀርመን ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ ኢራን ከአሜሪካን በቀጥታ እንድትደራደር ሃሳብ አቅርበዋል።

Sicherheitskonferenz München Sicherheitsvorkehrungen
ምስል Reuters

ባይደን በዚሁ ቃለ ምልልስ ኢራን ያቋረጠችውን የኒዩክልየር መርሃ ግብሯ ላይ የሚካሄደውን ድርድር እንድትቀጥልም መገፋፋታቸው ተዘግቧል።

ለሶስት ቀናት በሚቆየዉ ጉባኤ የሚሳተፉት የአሜሪካኑ ምክትል ፕሬዝደንት ጆ ባይደን፤ ነገ ለጉባኤዉ ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። ከጉባኤዉ አስቀድመዉ ግን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ጋ ስለሁለቱ ሀገሮች እና ስለአዉሮጳ ኤኮኖሚያዊ ይዞታ መነጋገራቸዉ ተሰምቷል። ስለጉባኤዉ የጀርመን መገናኛ ብዙሃን ያነሷቸዉን ነጥቦች እንዲያጋራን የበርሊኑን ወኪላችንን ይልማ ኃይለሚካኤልን በስልክ አነጋግሬዋለሁ፤

ይልማ ኃይለሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ