ኤኮኖሚኢትዮጵያ
የመገበያያ ገንዘብ ቅያሬ አንድምታዎች
ማክሰኞ፣ መስከረም 5 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግስት ከ23 ዓመታት በኋላ የሀገሪቱ የገንዘብ ኖት መቀየሩና አዲስ የ200 ብር ኖት ማዘጋጀቱ ትላንት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጉዳይ ዙርያ ያነጋገርናቸው ዜጎችና የኢኮኖሚ ዘርፍ ምሁራን ለውጡ በአዎንታና በስጋት ተመልክተውታል፡፡ ሕገወጥነት ከመከላከል አኳያ የገንዘብ ኖት ቅያሪው መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል የሚሉ ያሉ ሲሆን በአንፃሩ የኢኮኖሚ መዛባት፣ የዋጋ ግሽበትና ሌሎች ችግሮች ይዞ እንዳይመጣ የሰጉም አልጠፉም፡፡ በሌላ በኩል በገንዘብ ኖት ላይ የተደረገው ለውጥ ከኢኮኖሚያዊ ይልቅ በአብዛኛው ፖለቲካዊ ዓላማ ያለው ሲሉ ያነጋገርናቸው አስተያየት ሰጪዎች ገልፀዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ዙርያ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎችና በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚ ምሁር ሚሊዮን ኃይለስላሴ አነጋግሯል።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
አዜብ ታደሰ