1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመስከረም 12 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና

Yohannes Gebre Egiziabher Tarakeቅዳሜ፣ መስከረም 12 2016

የዓለም ዜና በድምጽ

https://p.dw.com/p/4Wjbn

የመስከረም 12 ቀን 2016 ዓ.ም የዓለም ዜና በድምጽ

ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ አዲስ አበባ ውስጥ እየተነጋገሩ ነው። ኢትዮጵያ 4ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በተሳካ መልኩ ማጠናቀቋን ተከትሎ ግብጽ ሕገወጥ በማለት ጉዳዩን ተቃውማ ነበር።

በማዕከላዊ የሶማልያ ግዛት በቦምብ ፍንዳታ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን የሃገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ። ፍንዳታው በመኪና በተጠመደ ቦምብ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።

በናይጄሪያ መሳሪያ የታጠቁ ሽፍቶች ከ30 በላይ ስቪሎችን ማገታቸውን ተሰማ። ከታጋቾቹ 24ቱ ሴት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው ተብሏል።

የሮማው  ካቶሊክ ቤተክርስትያን ሊቀጳጳስ ፍራንሲስ አውሮጳውያን ስደተኞችን እንደወራሪ ማየት የለባቸውም አሉ። ይልቁንም መልካም አቀባበል ሊያደርጉላቸው ይገባል ሲሉም መክረዋል።

ዩክሬይን በጥቁር ባሕር የሩስያ የባሕር ሃይል ማዘዣ ጣቢያ ባካሄደችው የሚሳይል ጥቃት አንድ የባሕር ሃይል ከፍተኛ አዛዥን ጨምሮ በአስራዎቹ የሚቆጠሩ ወታደሮች መግደሏን አስታወቀች።

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ከዚሕ ዝግጅት ተጨማሪ

ከዚሕ ዝግጅት ተጨማሪ

Äthiopien Alamata City Gondar
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።