ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ከ60 በላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት እንዲሁም የሌሎች ተቋማት ተወካዮች ዛሬ በመቐለ ተገኝተው ከትግራይ ክልል ሲቪል ተቋማት አመራሮች ጋር ተወያዩ። የተቋማቱ የዛሬ የመቐለ ጉብኝት በጦርነቱ ምክንያት ለሁለት ዓመት ተቋርጦ የቆየ ማእከላቸው አዲስአበባ እና መቐለ ያደረጉ የሲቪል ተቋማት ግንኙነት ዳግም ያስጀመረ ተብሎለታል።
ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ የልደታ ማርያም ቤተክርስቲያን ዲያቆንን ገድለው ሌሎች 11 አገልጋዮችን ደግሞ አገቱ፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሰላሌ አገረስብከት እንደገለጸው በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ቤተክርስትያናት በችግር ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁመዋል፡፡
ከጆርጅ ሲ ማርሻል እስከ ጆን ፎስተር ዳላስ፣ ከሔንሪ ኪንሲንጀር እስከ ማድሊን ኦል ብራይት፣ ከሒላሪ ክሊተን እስከ ማይክ ፖምፒዮ የተቀያየሩት የአሜሪካ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች መካከለኛዉ ምስራቅን ተመላልሰዉበታል።ሰላም ለማስፈን በወርቃማ ቃላትና አረፍተ ነገሮች ቃል ገብተዋል።ብሊንከንም ደገሙት።ሰላም ግን እዚያ ምድር የለም
ሰሜን ኮርያ ለመጀመርያ ጊዜ በኮሮና ሰዉ መሞቱን ገለፀች። ይህ የሀገሪቱ መግለጫ የተሰማዉ ሰሜን ኮሪያ በዓለማችን የኮረና ወረርሽኝ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገሪቱ የኮቪድ ወረርሽኝ መሰራጨቱን በይፋ ካሳወቀች ከአንድ ቀን በኋላ መሆኑ ነዉ። ሀገሪቱ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በመላ ሰሜን ኮርያ ይዝዉዉር እገዳ ተጥሎአል።