ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ሰሞኑን ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥት በዋናነት አማራ ክልል እና አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ጋዜጠኞችን፣ የማኅበረሰብ አንቂዎችን እና ሌሎች ከአራት ሺህ በላይ የሆኑ ሰዎችን በጅምላ በማሰሩ የመብት ተሟጋቾች እና ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪዎች ብርቱ ነቀፋ እየሰነዘሩበት ነው።
ወደ ትግራይ የርዳታ እህል ሲያጓጉዙ የቆዩ በርካታ ተሸከርካሪዎች ከትግራይ ክልል እየተመለሱ መሆኑን የዓለም ምግብ መርኃ -ግብር ዐስታወቀ። ባለፈው ዓመት መጨረሻ እና በተያዘው ዓመት መጀመሪያ ወደ ትግራይ ክልል የርዳታ ቁሳቁሶችን ጭነው የገቡ ከ1000 በላይ የርዳታ ተሸከርካሪዎች ለጦርነት ውለዋል በሚል መንግስት በተደጋጋሚ ወቀሳ ማቅረቡ ይታወሳል።
የምዕራባውያን ሃገራትን ትኩረት የሳበው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት መንስኤ ሳይሆን እንዳልቀረ የሚገመተው የኔቶ በምሥራቅ አውሮጳ አባላቱን የማብዛት እንቅስቃሴ የተገታ አይመስልም። ለሩሲያ የምትጎራበተው ፊንላንድና ስዊድንም የኔቶ አባል ለመሆን መነሳታቸው በኪየቭ ሞስኮ መካከል የተጫረውን የጦርነት እሳት አድማስ እንዳያሰፋው የሚሰጉ ጥቂት አይደሉም።
በዓለማችን በምግብ እጦት በዓመት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ህጻናት እንደሚሞቱ ተነገረ። የተባበሩት መንግሥታት የህጻናት መርጃ ድርጅት «ዩኒሴፍ» ዛሬ ይፋ ባደረገዉ መረጃ በአሁኑ ወቅት በዓለማችን ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ፤ ወደ 45 ሚሊዮን ህጻናት በረሃብ እየተሰቃዩ ነዉ።
ሰሜን ኮርያ ለመጀመርያ ጊዜ በኮሮና ሰዉ መሞቱን ገለፀች። ይህ የሀገሪቱ መግለጫ የተሰማዉ ሰሜን ኮሪያ በዓለማችን የኮረና ወረርሽኝ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገሪቱ የኮቪድ ወረርሽኝ መሰራጨቱን በይፋ ካሳወቀች ከአንድ ቀን በኋላ መሆኑ ነዉ። ሀገሪቱ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በመላ ሰሜን ኮርያ ይዝዉዉር እገዳ ተጥሎአል።
የዕለቱን ዝግጅት ለማዳመጥ «የቀጥታ ሥርጭት ማድመጫ» የሚለውን ማገናኛ ይጫኑ
ኢየሩሳሌም ከጥንት ከተሞች አንዷ ናት፤ በዚያም ላይ አወዛጋቢ። ለአይሁድ፣ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች ኢየሩሳሌም ቅድስት ከተማ ናት። በዚህም ምክንያት እስከዛሬ በከተማዋ ጉዳይ ጭቅጭቅ አለ።