ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ግማሽ ሚሊዮን ነዋሪዎች በተፈናቀሉበት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ በዘንድሮ ክረምት ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በምርት ለመሸፈን መታቀዱን የክልሉ ግብርና ተፈጥሮ ሀብት ጽ/ቤት ዐአስታወቀ። እስካሁን 60ሺ ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ ለዶይቸ ቬለ (DW) ተናግረዋል፡
"አራት አይነት የገበያ መደቦችን" ይኖሩታል የተባለውን የኢትዮጵያ ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅን ለማቋቋም እስከ ሁለት አመት እንደሚወስድ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ባለ ድርሻ በሆነበት ገበያ "ትላልቅ የስቶክ ገበያዎች" ፍላጎት እንዳሳዩም ተገልጿል። ከኢትዮጵያ ኩባንያዎች የትኞቹ ይሳተፉ ይሆን?
የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የጋራ ፖርታል "ሥራ ፈጣሪዎችን ለመርዳት ሁሉንም የሥራ ሥነ-ምህዳራዊ ባለድርሻዎች የሚያገናኝና የኢንቨስትመንት ልምድን ለማሳደግ መሠረት የሚጥል ነው።" በማስተርካርድ ፋውንዴሽን የገንዘብ ድጋፍ በተደረገለት ፕሮጀክት ከ340 በላይ ጀማሪ ኩባንያዎች እና ወደ 62 ኢንቨስተሮች እንደሚገኙ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ጦርነት፣ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና የጸጥታ መጓደል የበረታባቸው ያለፉት ዓመታት የኢትዮጵያን ሥራ ተቋራጮችና የግንባታ ግብዓቶች ገበያውን ተፈታትነዋል። የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ከዓለም ገበያ ለሚሸምቷቸው ግብዓቶች የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ይቸግራቸዋል። ከኤኮኖሚያዊ ሁኔታው የተስማማ የዋጋ ክፍያ ማስተካከያ ጉዳይም ይነሳል
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በዲመርጆግ የነዳጅ ማጠራቀሚያ በትብብር ለመገንባት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራርሟል። ሥምምነቱ ገቢራዊ ከሆነ የሚገነባው ማጠራቀሚያ 270 ቶን ነዳጅ የመያዝ አቅም ይኖረዋል። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በ1.6 ቢሊዮን ዶላር 550 ኪሎ ሜትር የነዳጅ ማጓጓዣ ቧንቧ ለመገንባት የወጠኑት ዕቅድም አልተሳካም
የከተማ መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዐሥርት ዓመታት በመንግሥት፣ በግለሰቦችና በባለሃብቶች 7.2 ሚሊዮን ቤቶች በከተማና በገጠር እንደሚሠሩ ይፋ አደረገ። ሚኒስቴሩ የቤት ችግር ዜጎችን በእጅጉ እየፈተነ ለከፍተኛ ማኅበራዊ ምስልቅል ማጋለጡን ገልፆ ይገነባሉ ከተባሉት ቤቶች መካከል የመንግሥት የመገንባት ድርሻ ሃያ በመቶ መሆኑን ተናግሯል።
የዕለቱን ዝግጅት ለማዳመጥ «የቀጥታ ሥርጭት ማድመጫ» የሚለውን ማገናኛ ይጫኑ
በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ በየቀኑ የሚቀዳው እያንዳንዱ ስኒ ቡና፥ በተለይ ሴቶች ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ በማድረጉ ረገድ በምጣኔ ሀብቱ ላይ ትንሽም ቢሆን የሚፈይደው ነገር አለ።