1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ኤኮኖሚ

የስኳርና የደም ግፊት ሕመም መድኃኒቶች ማግኘት ፈታኝ ሆኗል

ረቡዕ፣ መጋቢት 12 2010

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ስኳር እና የደም ግፊትን ለመሳሰሉ ሕመሞች የሚታዘዙ መድኃኒቶችን ማግኘት ፈታኝ እየሆነ መምጣቱን በመድኃኒት ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ኢትዮጵያ ከውጭ አገራት የምትሸምታቸው መድኃኒቶች ከወትሮው በተለየ በገበያ ላይ ለማግኘት አዳጋች የሆነው በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ ነው የሚል ምክንያት ተሰጥቷቸዋል።

https://p.dw.com/p/2ujKA
Deutschland Diabetes (Symbolbild)
ምስል AP/J. Sarbach

ኢትዮጵያ ዉስጥ የስኳርና የደም ግፊት መድሐኒቶች አይገኝም

አዲስ አበባ በሚገኙ ስምንት የመድኃኒት መደብሮች ለስኳር ሕሙማን የሚታዘዘው ሜትፎርሚን የተባለ መድሐኒት አይገኝም። ለደም ግፊት የሚታዘዘው ኒፊዲፒን የተባለ መድኃኒት ማግኘትም ይቸግራል። ለዚህ ዘገባ በ10 የመድኃኒት የመድሐኒት መደብሮች በመደወል ለማጣራት እንደሞከርንው ከሜትፎርሚን እና ኒፊዲፒን በተጨማሪ የተለያዩ መድኃኒቶች እጥረት በገበያው ላይ መኖሩን ለመታዘብ ችለናል። በመድኃኒት ገበያው ላይ የሚታየውን እጥረት የታዘቡ የፋርማሲ ባለሙያዎች እና የመድኃኒት መደብር ባለቤቶች ችግሩን ቢያረጋግጡም በይፋ ለመናገር ግን አይሹም። ሁሉም ግን አይደሉም። ላለፉት አራት ገደማ አመታት የመድሐኒት እጥረት ይታይ እንደነበር የሚናገሩት የፋርማሲ ባለሙያው አቶ ጸጋዬ ገብረየስ የአሁኑ ለየት እንዳለ ያስረዳሉ። ምክንያቱ ደግሞ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ነው። 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ

እሸቴ በቀለ

ኂሩት መለሰ