ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ፦ እጅግ ውብ ፉክክር በታየበት ግጥሚያ አርሰናል ማንቸስተር ዩናይትድን ድል በማድረግ ዘንድሮ ዋንጫውን ለማንሳት የቆረጠ መሆኑን ዐሳይቷል። ኧርሊንግ ኦላንድ በዘንድሮ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ለማንቸስተር ሲቲ አራተኛ ሔትትሪኩን ሠርቷል። በጀርመን ቡንደስሊጋ ቬርደር ብሬመን በኮሎኝ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል።
የኢትዮጵያውያን ድል ስለተስተጋጋባባቸው የአትሌቲክስ ውድድሮች፤ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንትና አመራር ምርጫ፤ የእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ፤ ቡንደስሊጋ፤ እና የሜዳ ቴኒስ ጨዋታ ላይ ዳሰሳ ይኖረናል።
እድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ኢትዮጵያውያት አዳጊ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ወደ ዓለም ዋንጫ ለመግባት ግስጋሴያቸውን ቀጥለዋል። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ አርሰናል ትናንት እጅግ ወሳኝ የሆነውን ድሉን አስመዝግቦ ደጋፊዎቹን በዓለም ዙሪያ አስቦርቋል። ማንቸስተር ሲቲ እና ሊቨርፑልም የፕሬሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ተፋጠዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በማላዊ ሜዳ ቆይታው ከወጪ ቀሪ አስልቶ «ትርፍ» ማስመዝገቡን ገልጧል። በርካቶች በሜዳችን እና በደጋፊያችን ፊት የበለጠ ድል ለመቀዳጀት ከደረጃ በታች ናቸው የተባሉ ስታዲየሞቻችን በአፋጣኝ መፍትኄ ይበጅላቸው ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።