ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊስን ያለመሸነፍ ጉዞ ትናንት መግታት ችሏል። የእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ አስደማሚ እና ልብ አንጠልጣይ በሆነ መልኩ ትናንት ሲጠናቀቅ ማንቸስተር ሲቲ ሲመኘው የነበረውን ዋንጫ በእጁ አስገብቷል። ሊቨርፑል በመጨረሻውና በወሳኙ ፌሽታ በሻምፒዮንስ ሊግ መፈንደቅ ይችል እንደሁ አምስት ቀናት መጠበቅ ይኖርበታል።
እድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ኢትዮጵያውያት አዳጊ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ወደ ዓለም ዋንጫ ለመግባት ግስጋሴያቸውን ቀጥለዋል። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ አርሰናል ትናንት እጅግ ወሳኝ የሆነውን ድሉን አስመዝግቦ ደጋፊዎቹን በዓለም ዙሪያ አስቦርቋል። ማንቸስተር ሲቲ እና ሊቨርፑልም የፕሬሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ተፋጠዋል።
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በተደረጉ የማራቶን የሩጫ ፉክክሮች ድል ተቀዳጅተዋል። ባለፈው ሳምንት አዲስ የተወለደ ልጁን በሞት ያጣው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ወደ ሜዳ ተመልሶ በፕሬሚየር ሊግ ለማንቸስተር ዩናይትድ 100ኛ ግቡን አስቆጥሯል። ነገ እና እና ከነገ በስተያ የሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ ወሳኝ ግጥሚያዎች ይኖራሉ።