ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በሸገር ከተማ የመስጂዶች ፈረሳ የፈጠረውን ቀውስ ለመፍታት የተደረገው ውይይት፤ በአሰቃቂ ሁኔታ የሚገደሉ ሰዎች የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስልና ከወደ ዚምባብዌ በፎቶ ብቅ ያሉት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በሣምንቱ መነጋገሪያ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል ናቸው። በዚህ ሣምንት በሞት የተለዩት ሻለቃ ባሻ አሊ በርኬ ጀግንነት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ተወስቷል።
የኦሮምያ ክልል መንግሥት በክልሉ ለሚደረገዉ የሰላም ጥረት ድጋፍ መጠየቁ፤ ስድስት ወራት የሞሉት የፕሪቶርያ ስምምነት አተገባበር ፍጥነት ይጎድለዋል መባሉ፤ ጉምቱዉ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌዉ ወደ ሃገር ቤት ሊመለሱ መሆኑ እንዲሁም በ 32 ቋንቋዎች የሚራጨዉ ዶቼ ቬለ 70ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑ በተሰኙ ርዕሶች ስር የተሰጡ ርዕሶችን ጨምቀን ይዘናል።
ለሰላም ድርድሩ መሳካት እዉቅና የተሰጣቸዉ ሰዎች ጉዳይ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት «ኦነግ ሸኔ» ከሚለው እና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከሚለው ታጣቂ ቡድን ጋር የሚያደርገው የሰላም ድርድር ፣የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች የመቀሌ ጉብኝት እንዲሁም የሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ በዚህ ሳምንት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ያነጋገሩ ጉዳዮች ናቸው።
ከፍተኛ የበጀት ክፍተት ገጥሞኛል ያለው እና በበርካታ ጫና ውስጥ ተሰንጎ የሚገኘው መንግስት በሰፋፊ እርሻዎች ስኬታማ እንደሆነ፤ ብሎም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ገንዘቦችን የሚጠይቁ ግዙፍ ፕሮጄክቶችን ለመተግበር እየጣረ መሆኑን ይገልጻል ።