ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። ስለዚሁ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎችን ከሰነድ አጠባበቅ መግለጫችን ማግኘት ይችላሉ።
በዛሬው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ቅኝት መሰናዶ፦ የሰሜን ሸዋው ጥቃት፤ የሲኖዶስ ሕገወጥ የጳጳሳት ሹመት የቀሰቀሰው ቁጣ እንዲሁም የአቶ በረከት ስምዖን መፈታት ላይ እናተኩራለን። አስተያየቶቻችሁ የተሰባሰበበትን ጥንቅር ሙሉ ዘገባ በድምፅ ማድመጥ ይቻላል።
በአዲስ አበባ የቤቶች ፈረሳ በቅጽበት ቤት አልባ ያደረጋቸው ነዋሪዎችን በእንባ አራጭቷል፤ ሕጻናት ተማሪዎች፤ እናቶችና አረጋውያንንም ለጎዳና መዳረጉ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ተጠቃሚዎች አነጋጋሪ ሆኗል ። የከተማዪቱ ከንቲባ «ከፍተኛ ፍልሰት»ን «መንግሥትን በመጣል በኃይል ሥልጣን» ከመቆጣጠር ጋር አያይዘው መናገራቸው በርካቶችን አስቆጥቷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ የወሰን አከላለል፣የመንግስት የሰላም የድርድር ምክረ ሃሳብ እና የህወሃት ክስ እንዲሁም በደቡብ ክልል የተነሳው የክልልነት ጥያቄ እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ በዚሀ ሳምንት በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በርከት ያሉ አእስተያየቶች የተሰጡባቸው ጉዳዮች ናቸው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስና «የኦሮሚያና ብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ» በማቋቋማቸው በተወገዙት ሦስት ሊቃነ ጳጳሳት መካከል የተፈጠረው ችግር በቤተክርስቲያኗ ቀኖና መሰረት ተፈቷል ሲሉ ብጹእ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዛሬ ማምሻውን አስታውቀዋል።